ውድ ጓደኞቼ፤
የሞንትጎመሪ ካውንቲ በኋይት ሃውስ አማካኝነት በተፈጸመው የፌደራል ሰራተኞች ቅነሳ እና አጠቃላይ ምስቅልቅል ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የካውንቲውን ነዋሪዎች እና ቤተሰቦችን ማገዙን አጠናክሮ በመቀጠል ላይ ይገኛል።
ባለፈው ሳምንት በሲልቨር ስፕሪንግ በሜሪላንድ ስቴት እና በበታች የአካባቢያዊ አካላት አዘጋጅነት የተካሄደው የስራቅጥር ኤግዚቢሽን በአካባቢ እና በስቴት ደረጃ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ውስጥ ከሚገኙ ቀጣሪዎች ጋር ለመገናኘት በሚፈልጉ የስራ ፈላጊዎች ተሞልቶ ነበር የሰነበተው። በነዚህ ክስተቶች መገኘት አልቻሉ ከሆነ ሌሎች ተመሳሳይ ዝግጅቶች ላይ ለመካፈል በአካባቢያችን ዙሪያ የሚገኙ የስራ እድሎች እና የመረጃ ኤግዚቢሽኖች የሚለውን ድረገጽ ይጫኑ።
ካውንስሉ በአሁኑ ጊዜ ለአገልግሎት እና እገዛ እንተባበር የዌቢናር ስብሰዎችን በየሁለት ሳምንቱ ማዘጋጀቱን የቀጠለ ሲሆን በዚህም ዌቢናር ላይ የካውንቲው ነዋሪዎች የሚፈልጓቸውን እገዛዎች በተገቢው መልኩ እንዲያገኙ የሚረዱ ከተለያዩ ባለሞያዎች የሚሰጡ ሃሳቦች፣ የመረጃ ሃብቶች፣ እንዲሁም በተለያዩ በጣም ጠቃሚ የሆኑ አርእስቶች ላይ የሚያተኩር ውይይቶች ይደረጋሉ።
ቀጣዩ ዌቢናር የሚካሄደው ዛሬ በ 11:30 ኤ ኤም ሲሆን በካውንስል አባል ናታሊ ፋኒ ጎንዛሌዝ አስተናባሪነት የሚካሄድ እና በተለይ የሚያተኩረውም የሞንትጎመሪ ካውንቲ የኢንተርፕረነርሺፕ ስነምህዳር/ኢኮሲስተም፤ የቢዝነስ ስራ ፈጣሪዎች እና ለፌደራል ተቀጣሪ ሰራተኞች የሚያስገኙት እደል በሚለው ርእስ ላይ ይሆናል። ዛሬ በ 11:30 ኤ ኤም ላይ በዙም በሚካሄደው ወቢናር ላይ ለመሳተፍ በዚህ ድረገጽ ይመዝገቡ። ዛሬ መሳተፍ ካልቻሉ የዌቢናር ማካሄጃ ሙሉ ፕሮግራሙን ይህን የካውንስሉን የዩትዩብ ገጽ በመክፈት ዝርዝሩን ማግኘት ይችላሉ።
ይህንን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ በምንጣጣርበት በዚህ ወቅት እርስ በርሳችን በመደጋገፍ፣ ጎሬቤቶቻችንን በመንከባከብ እንዲሁም አብረን በመስራት እና በመተባበር ይሄን ጊዜ በጋራ በመሆን እንወጣዋለን - ይህ ነው የሞንትጎመሪ ካውንቲ የሁልጊዜም አካሄድ።
እናንተን ለማገልገል ዝግጁ ነኝ፤
ኬት ስቴዋርት
የካውንስል ፕሬዚደንት
ባለፈው ሳምንት ከሜሪላንድ የላቲኖ ተወካይ ቡድን/ ኮከስ ጋር አብሬ በመሆን ፣ ከላቲኖ መሪዎች፣ በህዝብ ከተመረጡ ባለስልጣናት፣ እንዲሁም በመቶዎች ከሚቆጠሩ ነዋሪዎች ጋር አንድ ላይ በመሆን ሴኔተር ክሪስ ቫን ሆለን የህግ መብቱን ባልጠበቀ መልኩ ባለፈው ወር ከሃገር እንዲባረር የተደረገውን እንዲሁም የትራምፕ አስተዳደር የፍርድ ቤቶችን ትእዛዝ ባለማክበር ሊመልሰው ፈቃደኛ ያልሆነውን ኪልማር ዲያጎ ጋርሲያን የተባለውን የሜሪላንድ ነዋሪ ወደ ቤቱ ለማስመጣት የሚያደርጉትን ተጋድሎ ለመደገፍ አብረን መቆማችንን አሳይተናል። በዚህ መልኩ መሰረታዊ የሆኑ ህገመንግስታዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አደጋ ላይ በሚወድቁበት ጊዜ ሁላችንም ድምጻችንን ማሰማት እና በታሪክ ፊት ከትክክለኛው ወገን መቆማችንን ማሳየት ይኖርብናል። ሴኔተር ክሪስ ቫን ሆለን ለሚያደርጉት ልበ ሙሉነት የተሞላው አመራር አመሰግናቸዋለሁ።

በቅርቡ በተካሄዱ አሚስት የበጀት ህዝባዊ ክርክሮች ላይ 230 ነዋሪዎች በአካል ተገኝተው ምስክርነት የሰጡ ሲሆን በመቶዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ ሰዎች ደግሞ በጽሁፍ፣ በድምጽ እና በቪዲዮ ምስል ምስክርነት እና አስተያየታቸውን አቅርበዋል። ሁላችሁም በህዝባዊ ክርክሩ ላይ በአካል ለተገኛችሁ፤ በድረገጽ/ኦንላይን ለተከታተላችሁ እና በአጠቃላይ ሂደቱ ላይ ሃሳባችሁን ላካፈላችሁ ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ለ2026 አ ም የተመደበውን የ7.7 ቢሊዮን ዶላር የስራማስኬጃ በጀት በተመለከተ በተለያዩ ኮሚቴዎች አማካኝነት በመከራከር እና በምንሰጣቸው አስቸጋሪ የሆኑ ውሳኔዎች እና አጠቃላይ ሂደት ላይ የናንተ ግብረመልስ እና አስተያየት ዕገዛ እንደሚያደርግልን ለመግለጽ እንወዳለን።
የሞንትጎመሪ ካውንቲ በአሁኑ ሰአት በበተዝዳ፣ በሲልቨርስፕሪንግ እና ዊተን አካባቢ ለሚኖሩ ቤት አልባዎች እንክብካቤ ለሚሰጡ እና መስፈርቱን ለሚያሟሉ የህጻናት እንክብካቤ ሰጪዎች የቅናሽ የመኪና ማቆሚያ ፈቃድ በመስጠት ላይ ይገኛል። ይህን አስፈላጊ ለሆኑ የአገልግሎት ሰጪዎች ወጪ ለመቀነስ የሚረዳ አሰራር ከጅምሩ ጀምሮ የመራሁት እኔ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል። ለህብረተሰባችን እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን ለሚያቀርቡ አካላት ተመጣጣኝ እና በቀላሉ ተደራሽነት ያለው የትራንስፖርት አማራጭ ማቅረብ የነሱን በጎ ስራ ማገዝ የምንችልበት አንዱ መንገድ ነው። ተጨማሪ መረጃ እዚህ ያግኙ.
የሞንትጎመሪ ካውንቲ በጥሪ/ኦን ኮል የኤሌክትሮኒክስ እና የባትሪዎችን የመሰብሰብ ስራን በማካተት የጠርዝ ላይ የእንደገና ጥቅም ላይ የማዋል ፕሮግራምን በማስፋፋት ላይ ይገኛል። ይህ አገልግሎት ገና እየተጀመረ ሲሆን ከካውንቲው የእንደገና ጥቅም ላይ የማዋል አገልግሎት እያገኙ ላሉ ተጠቃሚ ነዋሪዎች የጥሪ አገልግሎቱ በታህሳስ 1 2025 እንደሚጀምር ይጠበቃል። የመሰብሰብ የጥሪ አገልግሎት ቀጠሮ ከማስያዝዎ በፊት ፕሮግራሙ ስለመጀመሩ በፖስታ ማሳወቂያ ደብዳቤ ሊደርስዎት ይገባል።ያስታውሱ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች እና ባትሪዎች በጠርዝ ላይ በሚገኙ የእንደገና ጥቅም ላይ የሚውሉ እቃዎች ማከማቻ ላይ ወይንም ከመደበኛ ቆሻሻ ጋር መቀላቀል አይችሉም፤ ምክንያቱም እሳት የማስነሳት አደጋ/ስጋት ስለሚያመጡ ነው! ለተጨማሪ መረጃ እዚህ ይጫኑ.

የሞንትጎመሪ የፕላን መምሪያ በሰኔ ወር ለሚጀመረው የማህበረሰብ የፕላን አካዳሚ የምዝገባ ጥያቄ ፎርሞችን እየተቀበለ ይገኛል። በመሆኑም በአካባቢዎ ስለሚተገበር የፕላን አወጣጥ ሂደት እንዲሁም ስለ ዞን አከላለል፣ ስለማስተር ፕላን አወጣጥ እንዲሁም ሌሎች ማህበረሰቡ ላይ ተጸኖ ስለሚያሳድሩ ቁልፍ ጉዳዮች ማወቅ ጥቅም ይኖረዋል። በመጭው የፎል/መሀር ወቅት በአጠቃላይ ካውንቲው ውስጥ ተለቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት ያለዎትን አስተያየት እና ግብረመልስ በመለገስ በፕሮግራሙ አቀራረጽ ላይ የራሥዎን ሚና በመጫወት በዛውም እንዴት ለመኖሪያ አካባቢዎ በጎ አስተዋጾ ማበርከት እንደሚችሉ ማወቅ ይችላሉ። እዚህ በመጫን montgomeryplanning.org/planningacademy ዛሬውኑ ይመዝገቡ!
የማህበረሰብ አባላት ከአሁን ጀምሮ ለክለሳ ክፍት በሆኑ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ ፖሊሲዎች ላይ አስተያየታቸውን መስጠት ይችላሉ። ይህን ሂደት ለህዝብ ክፍት ማድረግ መምሪያው የሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ከማህበረሰቡ ፍላጎት ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ያስችለዋል። የበለጠ ለማወቅ የመምሪያውን /MCPD/ ድረገጽ እዚህ ይጎብኙ.
በቅርቡ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ባካሄደው የከፍተኛ ደረጃ ስብሰባ ተካፍዬ የነበረ ሲሆን የስብሰባውም አላማ ለነዋሪዎቻችን የሃይል ወጪዎችን በማቃለል እና የአየር ብክለት ሊያስከትሉ የሚችሉ ጭሶችን በመቀነስ ረገድ ምን ያህል መሻሻል አሳይተናል የሚለውን ለመገምገም ነበር። ይህንን አመታዊ መድረክ በማዘጋጀት ነዋሪዎች፣ የሃይል ኤክስፐርቶች፤ እንዲሁም መንግስታዊ እና የግል የአጋር ድርጅቶች በቅርብ እንዲገናኙ በማድረጉ የአካባቢ ጥበቃ መምሪያው ሊመሰገን ይገባል!
የሞንትጎመሪ ካውንቲ የአረንጓዴ ፌስቲቫል /ግሪንፌስት በሞንትጎመሪ ካውንቲ የተመሰረተበትን 10ረኛ አመቱን ለማክበር ተዘጋጅቷል! ግሪንፌስት በሞንትጎመሪ ካውንቲ በየአመቱ የሚካሄድ እጅግ በጣም ጥልቁ ፌስቲቫል ነው። ግሪንፌስት 2025ን ቅዳሜ ሚያዝያ 26 ከ 11 ኤ ኤም እስከ - 4 ፒ ኤም ዊተን በሚገኘው በማሪያን ፍራየር ታውን ፕላዛ በመገኘት ቀጣይነት ያለው እድገትን፣ፈጠራን እና ለምለማማ/አረንጓዴ የሆነ አኗኗርን ያክብሩ! ለዝርዝሩ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ግሪንፌስት ድረገጽን ይጎብኙ.
የቫይብ ምርመራ/VIBE CHECKUP የሚባለው ሽልማት የተቸረው በወጣቶች የሚመራ ደህንነትን/ጤና ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ሲሆን አላማውም ለወጣቶች ወቅታዊ የሆኑ የአእምሮ ጤናን የተመለከቱ መረጃዎችና ሃብቶችን እንዲሁም አዳዲስ እራስን የመግለጫ እድሎችን እና የ አቻ ለአቻ እገዛ መድረኮችን ማመቻቸት ነው። በአሁኑ ሰአት እየተንቀሳቀሰ ያለው በሞንትጎመሪ ካውንቲ የመናፈሻ አካባቢዎች እና አራት የሞንትጎመሪ ካውንቲ የህዝብ ትምህርት ቤቶች ሲሆን አላማውም ተደራሽ የሆኑ የጤና እና አጋዥ የሆኑ የማህበራዊ ተሳትፎ መድረኮችን በማመቻቸት የወጣቶችን አቅም ማጎልበት እና ማበረታታት የሚል ነው። የቫይብ መፈለጊያ /ቸክ አፕ/ የሞባይል ስልክ አፕሊኬሽን በቅርቡ በአፕል እና በጎግል ፕሌይ ይለቀቃል።